company logo

የራዲዮ ፕሮግራም

arbegnoch_logo_dalas.jpg

የእርሶ ምርጫ

የወደፊት የኢትዮጵያን ዕድል የሚወሰነው?
 
arbegna foto 5-09-2004 084.JPG

Login Form



Content View Hits : 134143
10-09-2005

 
08-09-2005

 
የውጭ ጉዳይ

የኢሕአግ የቻፕተር ኮሚቴዎች ድጋፍ እያደረጉ ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በተለያዩ የአለም ሃገራት የሚገኙ የድጋፍ ኮሚቴ ቻፕተሮች ድጋፍ ማድረግ መጀመራቸውን የድርጅቱ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አስታወቀ።

ድርጅታችን ከአሁን በፊት ባካሄደው ኮንፈረንስ ላይ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት በየሀገራቱ ቻፕተሮች ተቋቁመው ተጠሪነታቸው ከድርጅቱ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ጋር መሆኑ የሚታወስ ሲሆን፣ በዚህም መሰረት እስከአሁን በጀርመን፣ በአውስትራሊያ፣ በኖርዎይ፣ በስዊድን ፣ በቤልጅየም፣ በካናዳ ተደራጅተው እንቅስቃሴ መጀመራቸው ይታወሳል።

Read more...
 
ወታደራዊ ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል::

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል::

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞ ግንባር ሰራዊት ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት ከቀናት በፊት በዋልድባ ሰቋርና አምቦ ጠበል ለሁለት ቀን ባደረገው ውጊያ 46 ገድሎ 64 ማቁሰሉን መዘገባችን ይታወቃል።

ጥቃቱ እንቅስቃሴውን በማስፋት በሚያዚያ 15-2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ከወያኔው ፈጥኖ ደራሽ ሐይልና ከፌደራል ጋር በተካሔደው ውጊያ በወረዳ አድርቃይ ልዩ ስሙ አሌ በተባለው ቦታ 17 የጠላት ቅጥረኞችን በመግደልና 24 በማቁሰል ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።

Read more...
 
መግለጫ

ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢ.ሕ.አ.ግ/

የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክና ማንነቱን ስንመረምር ሁሌም አስቀድሞ የሚታየን አትንኩኝ ባይነቱ ፣ ታጋሽነቱ፣ ብልሕና አስተዋይነቱ እንዲሁም ጀግንነቱ መቼም ቢሆን ከሕሊናችን የማይሰወር እውነታ ነው።

ይህ ኩሩና ጀግና ሕዝብ ላለፉት 21 ዓመታት ማንነቱን የሚፈታተኑ ኢ- ሰብዓዊና ኢ-ሞራላዊ የሆኑ አስከፊ ግፍና መከራን በሀይል እንዲቀበል አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ከመፈተን ለአንድም ደቂቃ ቢሆን ቦዝኖ አያውቅም።

የአካባቢ ምርጫ እየተባለ ለይምሰል ሁነኛ ተወዳዳሪ በሌለበትና የፖለቲካ ምሕዳር በጠበበት ሁኔታ ለግሉ በተቆጣጠረው ሚዲያ ለብቻው ተራ ድስኩር በሚያስተጋባበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር አገር አድን ሰራዊት በሚያዚያ 8ና በሚያዚያ 9-2005 ዓ.ም ታሪካዊውን የዋልድባ ገዳም ለማፍረስ ታች ላይ እያሉ በሚገኙ ሰራተኞች ጥብቃ እየተደረገ ከሚገኘው ከአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት ተመርጠው ከተውጣጡ የፈጥኖ ደራሽ ታጣቂ ሃይሎች ጋር ለ2 ቀን ባካሔደው ከፍተኛ ውጊያ የጠላትን አንገት ያስደፋ በአንጻሩ ወገንን ያኮራ ድል መቀዳጀቱ ይታወቃል።

Read more...
 
የኢሕአግ ሰራዊት በዋልድባ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በዋልድባ አካባቢ ልዩ ስሙ ሰቋር እና አምቦ ጠበል በተባለ ቦታ በተከታታይ ሁለት ቀናት ከወያኔው የፈጥኖ ደራሽ ጋር ባደረገው የፊት ለፊት ውጊያ በጠላት ላይ ወታደራዊ የበላይነትን በመቀዳጀት አኩሪ የአርበኝነት ጀብድ ፈፅሟል።

የግንባሩ ሰራዊት በዋልድባ ልዩ ስሙ ሰቋር በተባለ ቦታ በሚያዚያ 8-2005 ዓ.ም የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ መመኪያ በሆነው የፈጥኖ ደራሽ ላይ በከፈተው የማጥቃት እርምጃ 21 የጠላት ወታደሮችን በመግደል 25 ያቆሰለ ሲሆን፣ በተመሳሳይ በሚያዚያ 9-2005 ዓ.ም በዋልድባ ልዩ ስሙ አምቦ ጠበል በተባለው ቦታ ውጊያው የተካሄደ ሲሆን በዚሁ እለትም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት 25 የጠላት ወታደሮችን ገድሎ 39 በማቁሰል ከፍተኛ ድል የተቀዳጀ ሲሆን፣ በዚሁ አውደ-ውጊያ ላይም የተለያዩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያዎችንም ከመሰል ጥይቶቻቸው ጋር ማርኳል።

Read more...
 
ከአቶ የዋርካው መንግስቱ በአውስትራሊያ የኢህአግ ተጠሪ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ (ሜልበርን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ራዲዮ ጣቢያ)

 
በሰሜን ጎንደር መተማ

በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ሲሆን ፣ የወያኔ ካድሬዎችም ድርጊቱን ለማስቆም የተጠናከረ አሰሳ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለው የሕዝብ መነሳሳት ስሜትና ተጋድሎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከለውጥ ፈላጊው ሕዝብ ጎን የቆመ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያቶች በጠላት ላይ በሚያደርሰው ጥቃት የሀገርና የወገን ደራሽነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ከወታደራዊ ትግሉ ጎን ለጎን የአካባቢውን ህብረተሰብ የማስተማር፣ የመቀስቀስ፣ የማደራጀትና የማስታጠቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገለፀ።

በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኛች ግንባር ደጋፊዎች አማካኝነት የድርጅቱ ወቅታዊ የሀገር አድን ጥሪ በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ በመገኘቱ ስጋት የገባው አሸባሪው የወያኔ ገዥ ቡድን የቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ወከባና እንግልት እያደረሰ እንደሚገኝ ከስፍራው የደረሰን የመረጃ ምንጭ ያስረዳል።

Read more...
 
ወጣቱ ከአርበኛው ጎን ለመሰለፍ በረሃ እየገባ ነው

ሰራዊታችን ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ፡ብዛት ያላቸው ሴት ታጋዮችም ግንባሩን ተቀላቀሉ!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ነበልባል ጦር ጥር 17-2005 ዓ.ም በወልቃይት ጎብለል በተሰኘ የወያኔው መከላከያ ካምፕ ላይ በወሰደው ድንገተኛ ማጥቃት በካምፑ የሚገኙ የመከላከያ አባላትን ደምስሷል። በውጤቱም 25 ሙት 36 ቁስለኛ እንዲሁም 20 ክላሽንኮፍ ጠብመንጃ ፣ 4 የእጅ ቦንብና 1 ስናይፕር ጠብመንጃ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመማረክ በማግስቱ ማለትም በትናንተናው እለት በቀጠለው የነበልባል ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት በወልቃይት ጠበቆ በተባለ ቦታ 24 የአገዛዙ ታጣቂዎች ሙትና 29 ቁስለኛ ሆኗል። በድምሩ በሁለት ቀናት ውጊያ በጠቅላላው 49 ሙት 65 ቁስለኛ ሲሆን፦ የአምባገነኑ አገዛዝ ሰራዊት የአርበኛውን ጡጫ መቋቋም ተስኖት እግሬ አውጭኝ ብሎ ከመፈርጠጡም ባሻገር የውጊያ ሞራሉ ክፉኛ በመዳከሙ ምክንያት በአድጎሹ ፣ አደባይ፣ሁመራና እድሪስ አካባቢ የሚገኙ የጦር አመራሮች በመሰባሰብ የመልሶ መቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደተወጠሩ ታውቋል።

Read more...
 
አንፀባራቂ ድል እያስመዘገበ ይገኛል

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ጠገዴ በተለያዩ ቦታዎች

ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ።

የኢትዮጵያን ሕዝብ ከጎጠኛውና ከአሸባሪው የወያኔ አምባገነናዊ ስርዓት ለማላቀቅ የትጥቅ ትግልን አማራጭ አድርጎ ለሀገርና ለወገኑ መስዋዕትነት ለመክፈል ቆርጦ የተነሳው የኢትዮጵያሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት የፀረ- ወያኔ ትንቅንቁንና ፍልሚያውን አጠናክሮ በመቀጠል በተሰለፈባቸው አውደ- ውጊያዎች በጠላት ላይ ወታደራዊ የበላይነትን በመቀዳጀት የሐገርና የወገን አለኝታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል።

በዚህም መሰረት በታህሳስ 28 ቀን 2005 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ጠገዴ ሳርና በተባለ ቦታ ከልዩ ሃይል ታጣቂ ቡድን ጋር ከጧቱ 1፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ባደረገው ውጊያ 5 የጠላት ወታደሮችን በመግደል 13 ያቆሰለ ሲሆን በዝያው እለት ጠገዴ ጎርሶ በሚባል ስፍራ ከ11፡00 ሰዓት እስከ 12፡30 ባደረገው ውጊያ 3 የጠላት ወታደሮችን ገድሎ 5 አቁስሏል የግንባሩ ሰራዊት በዚሁ እለት ባደረገው ውጊያ በድምሩ 8 ገድሎ 18 በማቁሰል በጠላት ላይ አንፀባራቂ ድል አስመዝግቧል።

Read more...
 

Search

Latest Articles

  1. 10-09-2005
    (1999-11-30 00:00:00)
  2. 08-09-2005
    (1999-11-30 00:00:00)
  3. 06-09-2005
    (1999-11-30 00:00:00)
  4. 03-09-2005
    (1999-11-30 00:00:00)
  5. 01-09-2005
    (1999-11-30 00:00:00)



Copy right @2010 arbegnochginbar